ከሲዳማ ብሄራዊ ነጻነት ግንባርና ሲዳማ ስብአዊ መብቶች ካውንስል የተሰጠ መግለጫ!
ሚያዝያ 25 2019 አም
በኢትዮጵያ ለዘመናት ተንሰራፍቶ የቆየው የአምባገነኖችና የፋሽስቶች መንግስታት የወቅቱን የብልፅግና ስብስብ ጨምሮ የህዝብን መብትና ዲሞክራሲ አጥብቀው የምጠሉና የምደፈጥጡ ናቸው። ከዝህም የተነሳ የተለያዩ ብሄር ብሄረስቦችን እክልነትና መብት መቀበል ፈተና ሆኖባቸው አገርቷንም ለተከታታይ ጦርነቶችና አለመረጋጋት አጋልጠዋል። ሌላው የኢትዮጵያ ትልቁ ፈተና አገርቷ የብዙ ብሄር ብሄረስቦች አገር መሆኗን አለመቀበልና አንድ አይነት ማንነት ለመፍጠር መሞከር ሲሆን ይህም የሰውን ልጅ ሀይወት እንደሌለው አድርጎ በይዶ አንድ አይነት ቅርጽ ለመፍጠር እንደመሞከር ተድርጎ ይቆጠራል። ይህንን ተግባራዊ ለማድረግ የአብይ አረመኔ መንግስት በድብቅና በግልጥ የሚከተለው ፖሊሲ የመግደል፡ የብሄርስቦች እርስ በርስ ግጭቶችን መፍጠር፡ ከውጭ ሀይሎች ጋር በመተባበር ጦርነት አውጆ ህዝብን መጨፍጨፍና የህዝብን መብቶች በሴራና በተንኮል ጠልፎ ተቃዋሚዎችን ማጥፋት ብቻ ሳይሆን፡ ጦርነትን የህዝቡን ቁጥር መቀነሻ ዜዴ አድርጎ እየተጠቀመ ይገኛል። በተጨማሪም የኢትዮጵያን ብሄር ብሄረስቦች በጦርነት ብቻ ሳይሆን በመድሀኒት እጦትና ረሀብ ጭምር የአብይ አረመኔ መንግስት ሞት ፈርዶበታል፡፡
የሲዳማ ህዝብ ለማንነቱ ታገሎ የብዙ ወጣቶችን ህይወት መስዋእት አድርጎ የተካሄደው እልህ አስጨራሽ ትግል አለምም ጆሮውን ሰጥቶ ያዳመጠውና ያደነቀውን ረፈረንደም በ 98% ድጋፍ የራሱ ክልል እንድኖረው አድርጎታል። አምባገነናዊው የአብይ አህመድ መንግስት ይህን በህጌ መንግስቱ መርህ ላይ ተመስርቶ የተቋቋመውን ክልል የህጌ መንግስቱን መርሆዎች በመናድና ሌቦችና ፀረ ሲዳማ የሆኑ ወንጀኛ ካድረዎችን በህዝቡ ላይ በመጫን ለማፍረስ እየጣረ ይገኛል።
ይህ ክልል የሚፈርሰው በሲዳማ ህዝብ ሌላ ረፈራንደም ሲካሂድ ካልሆነ በስተቀር በምንምና በማንም ሀይል አይፈርስም። ይህንን ስንል አሁን የሲዳማ ህዝብ መብቱ ተከበረ ማለት አይደለም።
የራስን እድል በራስ የመወስን ጥያቄን በማዛባት የመገንጠል፡ የመለየት፡ ወይም የዘር ነው እያሉ ለማድበስበስ ይጥራሉ። ነገር ግን የህዝባችን ጥያቄ የዲሞክራሲ፡ የራሱን መሪዎች መምረጥና መሻር፡ ባህሉንና ቋንቋውን ብሎም ማንነቱን ማስከበር ሲሆን አሁንም ጸረዲሞክራሲያዊ ሀይሎች “በምስሌነ’’ ግፍና ምዝበራ እየመሩት ይገኛሉ። ህዝባችንና ብሄር ብሄረስቦች ከመቸውም ጊዜ በላይ ታፍነው ይገኛሉ። የሲዳማ ክልል ረፈርንድም ከተደረገ ወዲህ የራሱን መሪዎች አልመረጠም ። ዛሬም ሲዳማ ለሲዳማ መብትና ጥያቄ ባእድ በሆኑ እጅ ወድቆል። ዜግነትህን እኛ እንሰጥሀለን የሚሉ ሀይሎችን መስማት በሲዳማ የተለመደ ሆኖአል። ዜግነትን አካፋፋይ ኩባኒያ ሥር ሲዳማ መኖርን እንደማይቀበል በተደጋጋም ሰላማዊ በሆነ መንገድ አበክሮ ስገልጥ ቆይቶአል፡ ለአሃድዊ ሲዳማ ባንዳዎች ልገባቸው ባይችልም።
ዛሬ በሲዳማ ክልል በአሃድዊ ቅጥረኞች የሚካሄደው ሴራ የተሳስቱ ወሬዎችን በማስወራት ጎሳን ከጎሳ በማጋጨት የሲዳማን ምሁራን በመከፍፈል የህዝቡን አንድነት ለመበተን የምያደርገውን ጸረዲሞክራሲያዊ እንስቃሴ እያየን ነው። በጎሳና በሥልጣን ጥያቄ ስም የሲዳማን ክልል ለማክሽፍ የህግ በላይነት እንዳይኖር ለማድረግ እየተሰራ ያለው የአብይ ብልጽግና ዋናው ተለእኮ ነው። በተጨማርም በሀዋሳ ከተማ በልማት ስም ኢ-ፍትሀዊ በሆነ መንገድ የደሀ ቤቶች ማፍረስ ስብአዊነት የጎደለው አረመኔያዊ ተግባር ነው ብለን እናምናለን። ምስሊኔዎች የሀብታሞችን ፕሮጅክት ከውጭ አገር እየቀዱ ድሀውን ማፈናቀል ኢሰብአዊነትና ሂሊናብስነት ነው። የአብይ አረመኔ መንግስት ይህንንና ሌሎች ህገወጥ ወንጀል ለመፈጽም ለዝህም ነጻና ፍትሀዊ ምርጫ እንዳይደርግ በየአካባቢው የተጭበረበሩ የምርጫ ውጠቶችን በማስመዝገብ አሽንፈያለሁ በማለት የህዝቡን መብት ለመግፈፍ ሩጫ ላይ ይገኛል.። ስለዝህም ተቃዋሚዎችን በማሰር ቢሮአቸውን በማሸግ ላይ ተጠምዶ ይታያል።
በሲዳማም ጥቁር ባንዳዎችን (እነ ታሪኩ ለማንና ሌሎችንም) አንድሁም ነጭ ባንዳዎች (ደስታ ለዳሞ፡ አብርሀም ማርሻሎንና ሌሎችንም) በመጠቀም ያንን አሃድዊ ሥርአት ከአምሳ አመት በፍት የቀበርነውን ለመመለስ እያደባ ይገኛል። የሲዳማ ህዝብ ከአሁን በኋላ የወደፍቱን ብርሀን የምያይ እንጂ በኢትዮጵያዊነት ዘፈን በመታለል መብቱንንና ነጻነቱን እንደማይሽጥ አጥብቀው ልያውቁ ይገባል። የአገርቷም ፖለቲከኞች ቆም ብለው ማሰብ አለባቸዋል፡፡ ስለዝህም በመጀመሪያ የአብይን አረመኔ መንግስት በማሰውገዱ ላይ የሲዳማ ታጋዮች አምነው እየተንቀሳቀሱ ያሉ ሲሆን፡ ቀጣዩ ሁሉን አቃፍ ወደሆነው ዲሞክራሲያው ሥራአት መሸጋገር መሆኑን አጽእኖት ሰጥተው ህዝባቸውን ለትግል በማዘጋጀት ላይ መሆናቸውን ማሳወቅ እንወዳለ። በተጨማርም ሰላም ወዳድነታችን ብታወቅም ምን ጊዜም የመብታችንን ጠላቶች ረስተን አናውቅም። አንረሳቸውምም፡፡
ስለዝህም በመጨረሻ የሚከተሉትን ለሲዳማ ህዝብ ማሳወቅ እንወዳለን፡
1. በትግል የተጎናጸፍከውን ክልልና መብቶችህ እንዳይተገበሩ ያደረገው የዲሞክራሲ ጠላትህ አብይና ከእርሱ በመተባበር እድገትህንና ማንነትህን ሸጠው የበሉ የሲዳማ አመራር መሆናቸውን፡
2. በሀዋሳ የሚደረጉ የልማት እቅዶች የሲዳማን ህዝብ ያማከሉ መሆን ሲገባቸው የተዘረጋው ፖሊስ የተፈጥሮ ሀብትህንና መሬትህን እንደቀድሞ ንጉሳዊ ተላላኪዎች የማፈናቀል ዜይቤ ተከትለው አሁንም መሬትህን እየሸጡ እየለወጡ መሆናቸውን፡
3. የመሬት ባለቤትነት መብት ለመንሳት ኮርዶር በሚል ሀብቱን ወደ ፈዴራል ለማዛወር ‘በጥራቱ በየነ’ እየተሰራ ያለው የሴራ ፖለቲካ በልማት ስም ድሀን ማፈናቀል የሴረኛው ብልጥግና ዋናው መገለጫ ስለሆነ ሲዳማ አጥብቆ ልያውቀው እንደምገባ፡
4 የህዝብን መብት በመሽጥ የበለጸጉትን ባንዳዎች ለፍርድ መቅረባቸው የማይቀር ስልሆነ በየአካባቢይችሁ መረጃን በአግባቡ መሰብስብን፡
ሰላም ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያዊያን!!
ድል ለኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ሀይሎች!!
ሚያዝያ 25 2019 አም

Leave a Reply